ኢሳይያስ 13:1-22

  • በባቢሎን ላይ የተላለፈ ፍርድ (1-22)

    • “የይሖዋ ቀን ቀርቧል” (6)

    • ሜዶናውያን ባቢሎንን ይገለብጣሉ (17)

    • ባቢሎን ከዚያ በኋላ የሚቀመጥባት አይኖርም (20)

13  የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ+ በራእይ ያየው በባቢሎን ላይ የተላለፈ ፍርድ፦+   “በተራቆተ ዓለታማ ተራራ ላይ ምልክት* አቁሙ።+ ታላላቅ ሰዎች ወደሚገቡባቸው በሮች እንዲመጡድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ ጥሯቸው፤ እጃችሁንም አውለብልቡ።   እኔ ለሾምኳቸው* ትእዛዝ ሰጥቻለሁ።+ ቁጣዬን ለመግለጥበኩራት ሐሴት የሚያደርጉትን ተዋጊዎቼን ጠርቻለሁ።   ስሙ! በተራሮች ላይ እንደ ታላቅ ሕዝብ ድምፅ ያለየብዙ ሰዎች ድምፅ ይሰማል! አዳምጡ! አንድ ላይ የተሰበሰቡ መንግሥታትናብሔራት+ ሁካታ ይሰማል! የሠራዊት ጌታ ይሖዋ ሠራዊቱን ለጦርነት አሰልፏል።+   ይሖዋና የቁጣው መሣሪያዎችመላ ምድሪቱን ለመደምሰስ+ከሩቅ አገር፣+ከሰማያትም ዳርቻ እየመጡ ነው።   የይሖዋ ቀን ቀርቧልና ዋይ ዋይ በሉ! በዚያ ቀን ሁሉን ቻይ ከሆነው አምላክ ዘንድ ጥፋት ይመጣል።+   ከዚህም የተነሳ እጆች ሁሉ ይዝላሉ፤የሰዎችም ልብ ሁሉ በፍርሃት ይቀልጣል።+   ሰዎቹ እጅግ ተሸብረዋል።+ ምጥ እንደያዛት ሴትብርክና ሥቃይ ይዟቸዋል። እርስ በርሳቸው በታላቅ ድንጋጤ ይተያያሉ፤ፊታቸው በጭንቀት ቀልቷል።   እነሆ፣ የይሖዋ ቀን ምድሪቱን አስፈሪ ቦታ ለማድረግናበምድሪቱ ላይ ያሉትን ኃጢአተኞች ለማጥፋትበንዴትና በታላቅ ቁጣጨካኝ ሆኖ እየመጣ ነው።+ 10  የሰማያት ከዋክብትና የኅብረ ከዋክብት ስብስቦቻቸው*+ብርሃን አይሰጡም፤ፀሐይ ስትወጣ ትጨልማለች፤ጨረቃም ብርሃኗን አትሰጥም። 11  ምድሪቱን ስለ ክፋቷ፣+ክፉዎችንም ስለ በደላቸው እቀጣለሁ። የእብሪተኞችን ኩራት አጠፋለሁ፤የጨቋኞችንም ትዕቢት አዋርዳለሁ።+ 12  ሟች የሆነውን ሰው ከጠራ ወርቅ፣ሰዎችንም ከኦፊር ወርቅ+ ይበልጥ ብርቅ አደርጋለሁ።+ 13  ስለዚህ የሠራዊት ጌታ የይሖዋ ቁጣ በሚነድበት ቀን፣በታላቅ ቁጣ ሰማይን አናውጣለሁ፤ምድርንም ከቦታዋ አናጋለሁ።+ 14  እንደሚታደን የሜዳ ፍየል፣ እረኛም እንደሌለው መንጋእያንዳንዱ ወደ ወገኑ ይመለሳል፤እያንዳንዱም ወደ አገሩ ይሸሻል።+ 15  የተገኘ ሁሉ ይወጋል፤የተያዘም ሁሉ በሰይፍ ይወድቃል።+ 16  ልጆቻቸው ዓይናቸው እያየ ይጨፈጨፋሉ፤+ቤታቸው ይዘረፋል፤ሚስቶቻቸውም ተገደው ይደፈራሉ። 17  እነሆ፣ ለብር ደንታ የሌላቸውን፣በወርቅም ደስ የማይሰኙትንሜዶናውያንን አስነሳባቸዋለሁ።+ 18  ቀስታቸው ወጣቶችን ይፈጃል፤+ለማህፀን ፍሬ አያዝኑም፤ለልጆችም አይራሩም። 19  ከመንግሥታትም ሁሉ እጅግ የከበረችው፣*+የከለዳውያን ውበትና ኩራት የሆነችው ባቢሎን፣+አምላክ እንደገለበጣቸው እንደ ሰዶምና እንደ ገሞራ ትሆናለች።+ 20  ከዚያ በኋላ የሚቀመጥባት አይኖርም፤እንዲሁም ከትውልድ እስከ ትውልድ ድረስ የመኖሪያ ቦታ አትሆንም።+ በዚያም ዓረብ ድንኳኑን አይተክልም፤እረኞችም መንጎቻቸውን በዚያ አያሳርፉም። 21  የበረሃ ፍጥረታት በዚያ ይተኛሉ፤ቤቶቻቸው በጉጉቶች ይሞላሉ። ሰጎኖች በዚያ ይኖራሉ፤+የዱር ፍየሎችም* በዚያ ይፈነጫሉ። 22  የሚያላዝኑ ፍጥረታት በማማዎቿ፣ቀበሮዎችም በሚያማምሩ ቤተ መንግሥቶቿ ውስጥ ሆነው ይጮኻሉ። ጊዜዋ ቀርቧል፤ ቀኖቿም አይራዘሙም።”+

የግርጌ ማስታወሻዎች

ወይም “ለምልክት የሚተከል ምሰሶ።”
ቃል በቃል “ለቅዱሳኔ።”
ቃል በቃል “የእነሱ ከሲል።” ኦርዮንንና በዙሪያው ያሉትን የኅብረ ከዋክብት ስብስቦች ሊያመለክት ይችላል።
ወይም “የመንግሥታት ጌጥ የሆነችው።”
“ፍየል የሚመስሉ አጋንንትም” ማለትም ሊሆን ይችላል።